Sunday, May 13, 2012

የሰላምና አንድነት መልእክት የሚያስፈጽሙ ልዑካንን ወደ አዲስ አበባና ወደ ሰሜን አሜሪካ ተልከዋል።

"ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተ ክርስቲያን”  “ስለ ቤተ ክርስቲያን ሰላም ጸልዩ"

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ በወርሐ ግንቦት 2004 ዓ/ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የቤተ ክርስቲያናችንን የሰላምና አንድነት መልእክት የሚያስፈጽሙ ልዑካንን ወደ አዲስ አበባና ወደ ሰሜን አሜሪካ  ልኳል።

 ወደ አዲስ አበባ የተላኩት መምህር አንዱ ዓለም ዳግማዊ ሲሆኑ፣ በውጭ ሀገር በዋሽንግተን ዲሲ ወደ ተካሄደው ቅ/ ሲኖዶስ ደግሞ  አባ ጽጌ ድንግል ደገፉው ፥ ሊ/ማ  ዶ/ር አማረ ካሣዬ እና መምህር ልዑለ ቃል አካሉ ተልከዋል።

ጉባኤው ልዑካኑን የላከው በአሪዞና ከተማ የተካሄደውን የሁለተኛውን ዙር ጉባኤ አበው ሪፖርት የያዘ ደብዳቤና ለአባቶችና ለቤተ ክርስቲያን አንድነትና ሰላም ይጠቅማሉ ብሎ ጉባኤው ያመነባቸውን ባለሰባት ነጥብ የመፍትሔ ሐሳበችን እንዲያደርሱና ከጉባኤው የሚነሱትን ጥያቄዎች ጉባኤውን ወክለው እንዲመልሱ ነው። ጉባኤው የመፍትሔ ሐሳቦቹ በሁለቱም ዘንድ ተቀባይነት ካገኙ ለቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ቀን መቃረብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል ብሎ ያምናል።

እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን አንድ በማድረግ ሕዝቡን ያጽናና ዘንድ ጸልዩ።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ

No comments:

Post a Comment