Thursday, December 6, 2012

የሰላም ድርድሩ ተጀምሯል

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት ለመፍታት የተጀመረው የሰላም ድርድር የተጀመረ ሲሆን የመጀመሪያ ቀን ውሎ ምን እንደሚመስል በሚቀጥለው መልክ አቅርበናል::የኢትዩጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትተከታዮች በሙሉ በጸሎት እንድትበረቱ የሰላምና አንድነት ጉባኤው ይማጸናል::

የመጀመ ቀን ውሎ

ጠዋት

ü  መርሐ ግብር መሪ / መ/ር አንዱዓለም ዳግማዊ ከሰላምና አንድነት ጉባኤው

ü  ጸሎተ ኪዳን ተደርሷል/ብብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ መሪነት

ü  የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በመላከ መንክራት ቀሲስ አንዱዓለም ይርዳው  

ü  ከዚህ ጉባኤ ምን እንደሚጠበቅ በቆሞስ አባ ጽጌ ደገፋው  ባለ አምስት ነጥብ ማብራሪያ አቅርበዋል::

ü  የሰላምና  አንድነት ጉባኤው አባላት ትውውቅ ተደርጓል

ü  የመግቢያ መልዕክት በብፁዕ አቡነ ገሪማ  ቀርቧል

ብፁዕነታቸው በመልዕክታቸው እንደገለጹት ስለ ኢትዮጵያ  መጽሐፍ ቅዱስ የተናገረውን በመዘርዘር ኢትዮጵያ አገረ እግዚአብሔር መሆኗን አብራርተው ቤተ ክርስቲያን ለአገር ያበረከተችውን አስተዋጽኦ ዘርዝረው በተለያዩ ጊዜዎች ፈተና  እንደገጠማትና እንደተወጣችው  አብራርተዋል::ሰላም ማምጣት  አስፈላጊ መሆኑን ና ባፋጣኝ እንዲፈጸም አስረድተዋል::   

ü  ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅም ተመሳሳይ መልዕክት አስተላልፈዋል

ብፁዕነታቸው በመልዕክታቸው ታራቂዎችም አስታራቂዎችም እኛ ነን: ብለዋል::

 
ü  ከኢትዮጵያው ሲኖዶስና ከወጪው ሲኖዶስ የቀረቡትን ሁለት የመወያያ አጀንዳዎች በማጣጣም  በሰላምና  አንድነት ጉባኤው የቀረቡት ስድስት  የዕርቀ ሰላሙ የውይይት አጀንዳዎች እና  የመወያያ ደንብ ስለማጽደቅ የሚገልፀው ጹሑፍ በንባብ በመርሐ ግብር መሪው  ተነቦ ጉባኤው አጀንዳውን አጽድቋል::
ከሰዓት በኃላ

አወያይ ሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴ ዓለማየሁ::

ውይይቱ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ከሥልጣናቸው እንዴት ሊወርዱ እንደቻሉ የታሪክ ምስክርነታቸውን በወቅቱ በነበሩ ሁለቱም አባቶች ማለትም በኢትዮጵያው ሲኖዶስ ልዑካንና በውጪው ዓለም የሚገኘው ሲኖዶስ ልዑካን የታሪክ ምስክርነት ሰጥተው: ውይይቱ በሰላምና በፍቅር ቀጥሎ የዋለ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ወደ ኢትዮጵያ  መመለስ ባማስመልከት ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በይደር ተጠናቅቋል
ዝርዝሩን እንመለስበታለን
እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያናችንን አንድ ያድርግልን

 

No comments:

Post a Comment